FULLNESS OF CHRIST CHURCH (FCC)
IN MINNESOTA

የክርስቶስ ሙላት ቤተ ክርስቲያን በሚኒሶታ
“እርሷም ሁሉን ነገር በሁሉም ረገድ የሚሞላ የእርሱ ሙላቱ የሆነች አካሉ ናት።”  ኤፌ 1፡23
አድራሻችን (Our Address): 700 Diffley Rd, Eagan, MN 55123
Serving Ethiopian and Eritrean communities.

የክርስቶስ ሙላት ቤተክርስቲያን ተልእኮ

“አማኞችን በቅዱሳን ሀብረት ቤተሰባዊነትን በማጠንከር ጌታን እያመለኩ ፤ጸጋን እየተከፋፈሉና የክርስቶስን ወንጌል በማድረስ ደቀመዛሙርትን እያፈሩ ወደክርስቶስ ፍጹም ሙላት በባህርይና በእውቀት እንዲያድጉ ማድረግ ነው”


የክርስቶስ ሙላት ቤተክርስቲያ የአገልግሎት አላማ

እንደተሰጠን ጸጋ መጠን
∎ የእግዚአብሄርን ቃል በሙላት ማስተማር (ማቅረብ)
∎ የክርስቶስን ባህርይ ማወጅና አማኞች ባህሪውን አንዲመስሉ ማበረታታት
∎ የጸጋ ስጦታዎችን በማሳደግና አገልግሎት ላይ በማዋል አማኞች እንዲተናነጹ በማድረግ በህብረታችን ክርስቶስ ሙላት እንዲገለጥ ማበረታታት
∎ በእረኝነት አገልግሎት የቅዱሳንን መንፈሳዊ ህይወት መንከባከብና ማሳደግ
∎ ክርስቲያናዊ ህብረት የክርስቶስ ሙላት መገለጫ እንደሆነ በማወጅ ቤተሰባዊነትን ማጠናከርና ፍቅርን ማሳደግ
∎ ወንጌል ስርጭትን ማእከል ያደረገ የማህበረሰብ ተሳትፎን ማበረታታት


እሴቶቻችን
➣ ፀሎት፡- ምንም ነገር ከመስራታችን በፊት የጌታን ፊት መፈለግና ከእግዚአብሄርም ምሪትን መቀበልና የእግዚአብሔርን ፊት በጸሎት ማዘውተር 1 ተሰ 5:17-18

➣ ወንጌል ስርጭት ፡- በምድር ላይ የምንኖርበት ዋና አላማ ታላቁ ተልዕኮአችን እንደመሆኑ መጠን በአገኘነው አጋጣሚ ሁሉ በግልና በጋራ በቤተክርስቲያንና ከቤተክርስቲያን ውጪ የምስራቹን ቃል ለፍጥረት ሁሉ መስበክ፡ ማቴ 28:19-20

➣ ደቀመዝሙርነት ፤ ወንጌል ስርጭት ስኬታማነቱ ሚለካው የዳንኑት በደቀመዛሙርት አገልግሎት ራሳቸውን ችለው ሌሎችን በወንጌል መማረክ ሲችሉ ነው ስለዚህም በማስተማርና መምከር ደቀመዝሙር ለማደረግ እንተጋለን፡ማቴ 28:19-20

➣ ህብረት ፡ቅዱሳን በክርስቶስ የተመሰረተውን አንድነታቸውን ለማጠናከር ክርስቲያናዊ ህብረትን በመለማመድ ይታነጹ ዘንድ ህብረትን ማበረታታትና ማጠናከር እብ 10:24

➣ ፍቅር፤ የክርስቶስ ደቀመዝሙር መሆናችንን በፍቅራችን ለመግለጥ መትጋት ዬሀ 13:35 ሮሜ 15:5-6

➣ ትምህርት፡- የሁሉ ነገር መሰረቱ የእግዚአብሔር ቃል እውነት በመሆኑ አማኞች የእግዚአብሔርን ቃል በሙላትእንዲኖርባቸው በተለያየ ደረጃ ማስተማር

➣ ምህረትና ርህራሄ:- ድህነታችን በይቅርታ ላይ የተመሰረተ እንደመሆኑ እኛም ሰዎች በማንኛውም አይነት በደል ውስጥ በገኙ በየዋሃትመንፈስ በማቅናት ዳግም እንዲቆሙ በፍቅርና በርህራሄ መርዳት ፡ ኤፌ4:32 ቆላ 3:13

➣ ግልፅነት ፡- ማንኛውም የቤተክርስቲያኒቱን አሰራር፤ የገንዘብ አጠቃቀም ማለትም ገቢና ወጪ በየወቅቱ ለአባላት ማሳወቅ፡ ማቴ 25:21

➣ ታማኝነት ፡- ለእግዚአብሔርና ለእግዚአብሔር ህዝብ በጊዜ፤በአገልግሎትና በገንዘብ ታማኝ በመሆን ምሳሌነታችንን ለፍጥረት ሁሉ ማሳየት፡ሉቃ 12:42 ማቴ 25:21

➣ ሰዎች ሲፈልጉን መገኘት፡- አማኞችም ሆኑ ማንኛውም ሰው በማንኛውም ችግር ላይ የእኛን እርዳታ ሲፈልግ በማንኛውም ሰዓትና ቦታ በመድረስ አብሮነትን ማሣየት ገላ 5፡13

➣ ሎሌ አገልጋይነት፡- ከእግዚአብሔር የተቀበልነውን ህዝብ ዝቅ ብለን በባለደራነት መንፈስ እንደ አገልጋይ ሎሌ በታማኝነት የእግዚአብሔርን ህዝብ ማገልገል ፡ ገላ 5:15

➣ ተጠያቂነት፡- በእግዚአብሔርም ሆነ በህዝቡ ፊት ተጠያቂዎች እንደመሆናችን መጠን በነገር ሁሉ ምሳሌ በመሆን በቃልና በስራ በምናደርገው ነገር ሁሉ መጠንቀቅ ፡ማቴ 25:21

➣ አምልኮ፡- እግዚአብሔርን በእውነትና በመንፈስ በንፁህ ህሊና ድሃ አደጎችን፤ መበለቶችን፤ ወላጅ የሌላቸውን፤ ጎዳና ተዳዳሪዎችን አካለ ጎዶሎዎችን፤ ሴተኛ አዳሪዎችን በመርዳት እግዚአብሔርን ማክበር፡ ያእቆብ 1:27

➣ መከባበር፡- ሰው ሁሉ በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠረና ክርስቶስም የሞተለት ስለሆነ እርስ በእርሳችንም ሆነ ከሌሎች ጋር ባለን ግንኙነት ሰዎችን እግዚአብሔር እንደሚያያቸው በማየት ማክበር፡ሮሜ 15:14

➣ ሌሎችን መፈለግና አረኝነት አገልግሎት ፤ በክርስትና ህይወታቸው የደከሙ አማኞችንም ሆነ አዳዲስ ሰዎችን ዋጋ በመክፈል ያሉበት ድረስ በመሄድ መጎብኘትና ማበረታታት 1 ተሰ 3:13